6. የግብርናና ገጠር ልማት ሚኒስቴር ተግባርና ኃላፊነት
ግብርናን ማዕከል ያደረገው የገጠር ልማት ፖሊሲና ስትራቴጂያችን ተልዕኮ በዋናነት ግብዓትን፣ ምርትን፣ ግብይትን፣ ምርምርንና ኤክሰቴንሽንን በማቀናጀት በክፍለ-አኮኖሚው ዘላቂነት ያለው ሽግግር ማምጣት ሲሆን ራዕዩንና ተልዕኮዉም በአግባቡ ለቋፈፀም የሚከተሉት ሥልጣንና ተግባሮች እንዲኖሩት ተደርጓል፡፡
·
ፈጣንና ቀጣይነት ያለው የግብርናና የገጠር ልማት እንዲስፋፋ ያደርጋል፤
·
የመሬት አጠቃቀምና አስተዳደር ፖሊሲና የደንና የዱር እንስሳት ጥበቃና አጠቃቀም ሕጎችን ያዘጋጃል፤ አፈጻጸማቸውንም ይከታተላል፣ ያስተባብራል፤
·
የምግብ ዋስትና ፕሮግራምን ይመራል፣ ያስተባብራል፤
·
ለገበሬችና ለአርብቶአደሮች የሚሰጡ የኤክስቴንሽን አገልግሎቶች እንዲስፋፉ ያበረታታል፣ ድጋፍ ይሰጣል፤
·
የውሃ እቀባና አነስተኛ የመስኖ ልማት ሥራች እንዲስፋፉ ያበረታታል፣ ድጋፍ ይሰጣል፤
·
ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመተባበር የገጠር መሠረተ ልማት አገልግሎቶች እንዲስፋፉ ሁኔታችን ያመቻቻል፤
·
አግባብ ካላቸው አካላት ጋር በመተባበር የብድር አገልግሎቶች ለገበሬችና ለአርበቶአደሮች የሚቀርቡበትን ሁኔታ ያመቻቻል፤
·
በግብርና መስክ ለተሠማሩ የግል ባለሀብቶች የተሟላ ድጋፍ ይሰጣል፤
·
በግብርና ልማት ላይ ተፅአኖ የሚኖራቸውን ወቅታዊ ሁኔታች ይከታተላል፤ የቅድሚያ ማስጠንቀቂያ ሥርዓት ይዘረጋል፤
·
ወደ ሀገር በሚገቡትም ሆነ ከሀገር በሚወጡ ዕፅዋት፣ አዝርዕት፣ እንስሳትና የእንስሳት ተዋፅኦ ላይ ተገቢውን የኳራንቲን ቁጥጥር ያደርጋል፤
·
የእስሳትና የዕፅዋት በሽታች ወረርሽኝንና ተዛማች ተባዮችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር አስፈላጊውን እርምጃ ይወስዳል፤
የግብርና ልማት በገበያ እንዲመራና ቀልጣፋ የግብርና ግብዓትና ምርት ግብይት ሥርዓት እንዲፈጠር ለማድረግ፤
o
ገበሬች፣ አርብቶአደሮችና
በግብርና ልማት የተሠማሩ
ባለሀብቶች
በዋጋና በጥራት
ተወዳዳሪ ሊሆኑባቸው የሚችሉ ምርቶችን
መለየት እንዲችሉ
የገበያ ሁኔታችን
በተለይም የዓለም ገበያን በቅርብ እየተከታተለ የተሟላ፣ ወቅታዊና ትክክለኛ የገበያ መረጃ እንዲያኙ ያደርጋል፤
o
የዋና ዋና የግብርና ምርቶችና ግብዓቶች የገበያ ፍላጎት ትንበያ ጥናት ያካሂዳል፤ ውጤቱንም ለሚመለከታቸው ያሰራጫል፤
o
ለግብርና ግብዓት ግምገማና ማጽደቅ የሚረዱ መመሪያችንና የአሠራር ሥርዓቶችን ያወጣል፤ ሥራ ላይ መዋላቸውን ይከታተላል፤
o
የግብርና ግብዓት ጥራቱ ተጠብቆ ለተጠቃሚው መሰራጨቱን ያረጋግጣል፤
o
የግብርና ግብዓት ምርትን፣ አቅርቦትን፣ ሥርጭትንና ግብይትን አቅም ለመገንባት አስፈላጊውን እገዛ ያደርጋል፤
o
የግብርና ምርቶች ገበያ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የሚስፋፋበትን መንገድ ይቀይሳል፣ ተግባራዊ ያደርጋል፤
o
ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመተባበር የግብርና ምርቶች ገበያ ማዕከላት እንዲፈጠሩና እንዲጠናከሩ ሁኔታችን ያመቻቻል፤
o
የግብርና ምርቶች የጥራት ደረጃቸው ተለይቶ ለገበያ የሚቀርቡበት ሥርዓት እንዲኖር ለማድረግ ከኢትዮጵያ የጥራትና የደረጃች ባለሥልጣን ጋር ይተባበራል፤